Home 100 Days Performance Report
ማሰታወሻ፡
+ይህ ግምገማ በሁለተኛው መቶ ቀን ውስጥ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ አፈፃፀም የሚለካ በመሆኑ ሁሉንም የተቋሙን ተግባራት አያካትትም::
+ከዚህ በታች በመቶኛ የተገለፁት ቁጥሮች የብዙ ዝርዝር ተግባራት አማካኝ ውጤቶች ሲሆኑ ከታች የተገለፁት ግን የተመረጡ ዋና ዋና ተግባሮች ናቸው፡፡
ግንዛቤ መፍጠር |
92% |
---|---|
ህጎችን ማጠቃለል፣ ማሻሻልና በድህረ ገጽ መጫን ታቅዶ በአብዛኛው ተከናውኗል |
የአገልግሎት አሠጣጥ |
75% |
---|---|
በወቅቱ የቅሬታ ምላሽ የሚያገኙ ግብር ከፋዮችን ብዛት ወደ 90 በመቶ አድጓል | |
ለሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ታቅዶ በዋና ዋና 4 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የግብር ከፋይ አገልግሎት ጥራት ላይ መካከለኛ ወይም ከፍ ያለ እርካታ ያላቸው ግብር ከፋዮች ብዛት ወደ 82 በመቶ አድጓል |
ገቢ መሰብሰብ |
97% |
---|---|
59.9 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 50.8 ቢሊዮን ብር (85%) ተሰብስቧል | |
የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ ተጠቃሚዎችን ቁጥር አሁን ካለበት 82 በመቶ (160 ሺህ) ወደ 85 በመቶ (164ሺህ) ማሳደግ ታቅዶ 162 ሺህ (99%) ተከናውኗል |
ለህግ ተገዢነትን ማረጋገጥ |
82% |
---|---|
በህገ-ወጥ ተግበር ላይ ተሰማርተዉ ሃሰተኛ ደረሰኝ በሚጠቀሙ፣ ህጋዊ ያልሆነ የካሽ ሬጅስተር መሳሪያ ገዝተዉ ደረሰኝ በሚሰጡና በሚጠቀሙ እንዲሁም ያለአግባብ ተመላሽ በሚጠይቁ 45 ድርጅቶች ላይ እርምጃ መዉሰድ ታስቦ 135 ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዷል |
ምርትና ኤክስፖርት |
66% |
---|---|
ከወጪና ገቢ እቃዎች የጉምሩክ ስነስርዓት ለመፈፀም ይጠየቁ ከነበሩት ሰነዶች ውስጥ ከእያንዳንዳቸው 40 በመቶ መቀነስ ሙሉ በሙሉ ተከናውኗል | |
በጉምሩክ ዋጋ አተማመን (ECVS) ዙሪያ ያሉ ችግሮችን የመለየት፣ የማስተካከል እንዲሁም ለማልማት የተያዙ ሥራዎችን ሙለ ለሙሉ መፈፀም ታቅዶ ጥናት ተካሂዷል |
ሎጂስቲክስ |
63% |
---|---|
የስካኒንግ ማሽኖችን ቁጥር ከ6 ወደ 8 ለመጨመር ታስቦ ከነባሮቹ 4 በመበላሸታቸውና ሊጠገኑ ባለመቻላቸው፣ አዳዲሶቹም አገልግሎት ላይ ባለመዋላቸው አጠቃላይ የማሽኖቹ ቁጥር ቀንሷል | |
የኤርትራ ወደብ አገልግሎት ለመጀመር 6 ጽ/ቤቶ ለመክፈት ታቅዶ 6ቱም ተከፍተዋል |
ጠንካራ አፈጻጸም ያሳዩ | ደካማ አፈጻጸም ያሳዩ | ቀጣይ አቅጣጫዎች |
---|---|---|
▪ ገቢን ከመሰብሰብ አኳያ ከባለፈው መቶ ቀን በላቀ መልኩ (97%) ተከናውኗል ▪ የታክስ መረብንና የግብር ከፋዩን አገልግሎት ጥራት መለካቱ ገቢን ዕድገት ለማፋጠን የሚደረገው እንቅስቃሴ ሚዛናዊ እንዲሆን ያግዛል |
▪ በዛ ያሉ የህግ ማሻሻያ ሥራዎች ቢሰሩም በተጨባጭ ያመጡት ውጤት ካልተለካ እንደውጤት ማየት ያስቸግራል ▪ የግብር ከፋይ አገልግሎትን መለካት ቁልፍ ሥራ በመሆኑ ቀጣይነት ሊኖረው፣ በሁሉም ቅርንጫፎች ሊካሄድ እና እውነተኛ ተዓማኝነት ያለው መረጃ መሰብሰቡን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ▪ በቴክኖሎጂ በኩል የታቀዱት ድርጊቶች ያስገኙት ውጤት ዝቅተኛ ነው። ለምሳሌ የECVSን ችግሮች በመፍታት ረገድ |
▪ በኦዲት እንደታየው የተገኘው ውጤት ከዕቅዱ በጣም ገዝፎ ሲገኝ የሥራው ጥራት ተጎድቶ እንዳይሆን መመርመር ይኖርበታል ▪ ህገ ወጥ የውጭ ንግድን አስመልክቶ ችግሮችን መለየት እንዲሁም ከማስተማርና ከማነቃቃት ውጭ ተጨባጭ እርምጃዎች ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትንም በተለይ ክልሎችን ማስተባበር ያስፈልጋል ▪ የታዩ የቴክኖሎጂ ችግሮችን ከመፍታት በተጨማሪ የቴክኖሎጂ አስተዳደር ሥርዓትና ብቃት መገንባት ትኩረት ይሰጠው |