የሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር

Home 100 Days Performance Report


ማሰታወሻ፡
+ይህ ግምገማ በሁለተኛው መቶ ቀን ውስጥ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ አፈፃፀም የሚለካ በመሆኑ ሁሉንም የተቋሙን ተግባራት አያካትትም::
+ከዚህ በታች በመቶኛ የተገለፁት ቁጥሮች የብዙ ዝርዝር ተግባራት አማካኝ ውጤቶች ሲሆኑ ከታች የተገለፁት ግን የተመረጡ ዋና ዋና ተግባሮች ናቸው፡፡

የሴቶች ዘርፍ

69%

በጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በተለይ ካለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛት በ 5 ክልሎች፣ 1 ከተማ አስተዳደር ፣ በ 20 ቀበሌዎች ነጻ መሆናቸውን ማረጋገጥና ዕውቅና መስጠት
ፆታዊ ጥቃት የደረሶባቸው 600 ሴቶችን የስራ እድል የሚያስችሉ ስራዎች መከናወን
50 ለሚሆኑ ህብረት ስራ ማህበራት እውቅና ለመስጠት መረጃዎችን የማደራጀት እና ያሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን በዶክመንተሪ ፊልም የመቀመር ስራ ተሰርቷል፣ በተጨማሪም 4.2 ቢሊዮን ብር የቆጠቡ ሴቶችን ወደ ዩኒየን እንዲሸጋገሩ የግንዛቤ እና ንቅናቄ ስራዎች ተሰርቷል
በኤርፖርቶች፣ ባለ 3 እና ከ 3 በላይ ኮከብ ሆቴሎች መሸጫ ያላቸውን እንዲሁም በእደ ጥበብ ስራ የተሰማሩ ሴቶችን መረጃ በማሰባሰብ ኤግዚቢሽኑን ለማዘጋጀት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተሰርቷል
ለአመራር ብቁ ሊሆኑ የሚችሉ ሴቶችን በመለየት የማብቃትና የሴት አመራሮች ቋት ለማዘጋጀት የሴቶችን የአመራር ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ለ150 ሴቶች መስጠት

የህጻናት እና የወጣቶች ዘርፍ

76%

በችግር ውስጥ የሚገኙ ህፃናት በተለያዩ ተቋማት 55,000 ህፃናት እንዲደገፉ ማድረግ
20 የህፃናት ማሳደጊያ ለማጠናከር 2 ሚልዮን ብር፣ የወጣቶች የስብዕና ልማት ማዕከላትን ለማጠናከር የሚያስችል 5 ሚሊዮን ብር፣ በችግር ውስጥ የሚገኙ ህፃናት ለመደገፍ 100 ሚልዮን ሀብት ሃብት ማሰባሰብ ስራዎችን ማከናወን
በአፋር 50፣ በጋምቤላ 50፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ 50፣ በኢ/ሱማሌ 50 በድምሩ 200 የማህበረሰብ አቀፍ ጥምረቶች እንዲቋቋሙ ማስተባበርና መደገፍ
ወጣቶች በስራ ፈጠራ፣ በስብዕና ልማትና በአገር ግንባታ ሂደት፣በሚኖራቸው ሚና ዙሪያ የፓናል ውይይት ማካሄድ
ሀገር አቀፍ የወጣቶች ፖሊሲን ለመከለስ የሚያስችል ተጨማሪ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ ፖሊሲውን መከለስ የሚያስችል ምክረ-ሃሳብ ማቅረብ ተችሏል
ጠንካራ አፈጻጸም ያሳዩ ደካማ አፈጻጸም ያሳዩ ቀጣይ አቅጣጫዎች

• ከሁሉም የኒቨርስቲዎች የተውጣጡ 147 ሴት ማህበራት አባላት በተገኙበት በሴቶች መብቶችና ጾታዊ ጥቃት መከላከል ዙሪያ አንድ የንቅናቄ መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡
• በችግር ውስጥ የሚገኙ ህፃናት በተለያዩ ተቋማት 55,000 ህፃናት እንዲደገፉ ተደር ጓል ፡፡
•ሃገር አቀፍ የወጣቶች ፖሊሲን ለመከለስ የሚያስችል ተጨማሪ የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል
•የንቅናቄ መድረኮችና ስልጠናዎች ተሰጥተዋል

• በጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ማለትም ያለዕድሜ ጋብቻና ሴት ልጅ ግርዛትን መቀነስ፤
• ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፤
• በአፋር 50፣ በጋምቤላ 50፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ 50፣ በኢ/ሱማሌ 50 በድምሩ 200 የማህበረሰብ አቀፍ ጥምረቶች እንዲቋቋሙ ማስተባበርና መደገፍ፣
• የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ፣ በስብዕና ልማትና በአገር ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ማስቻል፤

• በሴቶች ላይ የሚደረጉ ጾታዊ ትንኮሳን፣ የህግ ጥሰቶችንና ጎጂ ልማዳዊ ድረጊቶችን ከመከላከል፣ ከመቆጣጠር እና የህግ ማስከበር ስራ ከፌደራል አቃቢ ህግ ቢሮ ጋር በመተባበር በትኩረት መስራት፤
• የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሁሉም ኢኮኖሚ ሴክተሮች ተሳትፏቸውን ለማሳደግ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
• በህጻናት ላይ የሚደርሱ ህገ ወጥ የጉልበት ብዝበዛን፣ ጾታዊ ትንኮሳን እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር በዘላቂነት እንዲቋቋሙ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
• ለወጣቶች ስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ስራዎች ከሚመለከታቸዉ የመንግስት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት ስራዎች ይሰሩ፤
• ከሌሎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጋር በቅንጅት መስራት

የእርስዎ አስተያየት